የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ

የፀጥታ አካላት እና የባለድርሻ አካላትን፣ለሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች በማቀናጀት፣በማስተባበርና በመምራት እንዲሁም ሕብረተሰቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ የአዲስ አበባን ሰላም እናፀናለን!

ተልዕኮ

የተቀናጀ የጸጥታ ጉዳዮች አስተዳደር እና የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ወንጀልን በመከላከል፤ የሰላም እሴቶችን በመገንባት፣ በሃይማኖትና እምነት ተከታዮች መካከል መከባበርና መቻቻል እንዲሰፍን በማድረግ፤ የክትትል፤ ቁጥጥር እና ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት በመዘርጋት፣ ነዋሪውንና ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎና ባለቤትነት በማረጋገጥ ሰላም፣ ጸጥታና ደህንነቷ የተጠበቀ እና ህግና ስርዓት የተከበረባት ከተማ ማድረግ ነው፡

ራዕይ

በ 2022 አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነት ሰላምና ጸጥታ የሰፈነባት፤ የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት፣ ለኑሮ ለስራ እና ለመዝናኛ ተመራጭ የሆነች ከተማ ሆና ማየት

እሴቶች

የህግ የበላይነትን ማክበርና ማስከበር ፤ ለላቀ ሰላምና ጸጥታ መትጋት ፤ ታማኝነትና ተጠያቂነት ፤ ተቋማዊ አጋርነት ፤ ፍትሐዊነትና ሰብዓዊነት ፤ ሚስጥር ጠባቂነት

የቢሮው ስልጣንና ተግባር

1. የደንብ ማስከበር ባለሥልጣንን በበላይነት ይመራል፤ ያስተባብራል፤
2. ከተማ አቀፍ ፖሊሲ ይቀርፃል፤ ስትራቴጂ ይነድፋል፤ ህግ ያመነጫል፤ ሲጸድቅም ተግባራዊ መሆኑን ይከታተላል፤ ያረጋግጣል፤
3. በፀጥታ ጉዳዮች የከተማው አስተዳደር ዋና የፀጥታ አማካሪ ሆኖ ይሰራል፤
4. የግጭት መንስዔዎችን በጥናት ይለያል፣ ግጭት እንዳይከሰት ይከላከላል፤ ሲከሰትም ባህላዊና ዘመናዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን በመጠቀም ይፈታል፤
5. ሀይማኖትና ቤተ-እምነት ተከታዮች መካከል ሰላምና መከባበር እንዲሰፍን ለማድረግና ግጭትንም ለመከላከል እንዲቻል አግባብነት ካላቸዉ አካላት ጋር በመተባበር ይሠራል፤
6. ፀጥታ አጠባበቅ ጉዳዮች ዙሪያ አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር ችግሮችን በተናጠል ወይም በጋራ ይፈታል፤
7. ህግና ስርዓት መከበሩንና የህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት መጠበቁን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣
8. ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን፣ ቡድኖችንና ድርጅቶችን በመከታተል ነዋሪውንና ሌሎች የሚመለከታቸውን አካላት በማሳተፍ ይከላከላል፤ ይቆጣጠራል፤

አገልግሎቶች

ለብዙሃን ማህበራት እና አደረጃጀቶች የምዝገባና የድጋፍ አገልግሎት መስጠት

Read More

አዲስ የኃይማኖት ተቋማት ለሚመሰረቱ አካላት የሰላማዊነት ማረጋገጫ የመስጠት አገልግሎት

Read More

በመኖሪያ አካባቢ የሚፈጠሩ የድምጽ ብክለት ችግር ምላሽ የመስጠት አገልግሎት

Read More

ከግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች የአሰራር ስርዓት ጋር በተያያዘ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት

Read More

ፀጥታን የተመለከቱ መረጃዎች ለሚጠይቁ ተቋማት ምላሽ መስጠት

Read More

ለጦር መሳሪያ አጠቃቀምና አያያዝ ፍቃድ አስተዳደራዊ ድጋፍ መስጠት

Read More

አድራሻ

አዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ህንጻ ቁጥር ሁለተኛ ፎቅ 41፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

0115-11-22-33

peaceaddis123@gmail.com

Loading
Your message has been sent. Thank you!